Skip to content
Facebook
Twitter
Telegram
YouTube
Home
About us
Board Members & Teams
Profile
Products
Major product
By products
Co-products
Tender
Foreign
Local
Vacancy
wonji shoa sugar factory
About us
Board Members & Teams
By products
CO
Co-products
Foreign
Home
Jobs
Local
Major product
News
Products
Profile
Services
Tender
Vacancy
የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ የስራ መሪዎችና ሲኒየር ባለሙያዎች በእርሻ ዘርፍ የተከናወኑ ስራዎችን ጎበኙ፡፡
በፋብሪካው የ2017 ዓ.ም ምርት እቅድን ለማሳካት እየተደረገ የሚገኘዉን ዝግጅት አስመልክቶ በሸንኮራ አገዳ ማሳዎች ላይ በመዘዋወር የተጎበኘ ሲሆን በጉብኝቱ በድሬይኔጅ መስመሮች ጥገና የታየ ዉጤት ፣ የተጎዱ ማሳዎችን ከድሬይኔጅ በወጣ አፈር የማከም ስራ ያመጣዉ ዉጤት፣በእርሻ ዘርፍ የተከናወኑ የሌማት ትሩፋት የስራ እንቅስቃሴ፣ በተጓዳኝ ልማት የእንቁላል ዶሮዎች እርባታ ማእከል ፣የስንዴ ዘር ስራ፣ በከፍተኛ ጥረት የለማ የአዉት ግሮወርስ የሸንኮራ አገዳ ማሳዎች ቁመና ታይቶ ዉይይትም ተደርጎበታል፡፡ በመርሃግብሩ ከተሳታፊ ስራ ሃላፊዎችና ባለሙያዎች በተሰጠ አስተያየት አሁን የሚታየዉ የሸንኮራ አገዳ ማሳ ቁመና የተያዘዉን የስኳር ምርት እቅድን ለማሳካት የሚያስችል መሆኑን በደስታ እና በልበሙሉነት የገለጹ ሲሆን ለዚህ ተስፋ ሰጪ ስራ የስራ አመራር ቦርዱን እና ማኔጅመንቱን አመስግነዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ማጠቃለያ የፋብሪካዉ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጀማል አማን ባስተላለፉት መልዕክት በእርሻ ዘርፍ ይህ በማሳ ላይ አምሮ የሚታየዉን የሸንኮራ አገዳ ሳይባክን ፋብሪካ መድረስ እንዳለበት በመግለጽ በፋብሪካ ዘርፍ በኩልም አስፈላጊ ዝግጅት እንዲደረግ እና የተያዘዉን እቅድ ለማሳካት ሁሉም የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደርግ አሳስበዋል፡፡
Scroll to Top