Categories: 21/1/2023

በወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ለአባትና እናት ጡረተኞች የሸኝት መርሃ-ግብር ተካሄደ​

በወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ለአባትና እናት ጡረተኞች የሸኝት መርሃ-ግብር ተካሄደ

የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካን ከወጣትነት ዕድሜያቸው ጀምሮ ለረዥም ዓመታት በታማኝነት እና በቅንነት ሲያገለግሉ ቆይተው በዕድሜ ጣሪያ ምክንያት ከጥር 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በጡረታ የተሰናበቱ እናት እና አባት ጡረተኞች በወንጂ የሠራተኞች መዝናኛ ከበብ ሽኝት ተደረገላቸው፡፡

የዘንድሮው የሽኝት መርሃ-ግብር ከሌላው ጊዜ ለየት የሚያደርገው ፋብሪካው ሌሎች አምስት ስኳር ፋብሪካዎችን ጨምሮ በመንግስት በተላለፈ ውሳኔ መሰረት የስራ አመራር ቦርድ ተቋቁሞለት እራሱን ችሎ እንዲመራ በተወሰነ ማግስት መሆኑና በአዲስ ምዕራፍ የተለያዩ ስትራተጂዎችን ነድፎ ወደ ቀድሞ አቋሙ ለመመለስ በሚደረግ የባለሙያዎች ርብርብ እና የቅርብ ክትትል አመራር እየተሰጠ ባለበት ወቅት መሆኑ ነው፡፡

በዚህም የሽኝት መርሃ-ግብር የፋብሪካው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጀማል አማን፣ የኢትዮጲያ የስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ተወካይ አቶ ገበየሁ ማስረሻ እና ሌሎች አመራሮች ለጡረተኞቹ የምስክር ወረቀት አበርክተውላቸዋል፡፡

wssf

Recent Posts

በትውልድ አሻራ የተገነባ፣ የጥራት ምስክርነት

በትውልድ አሻራ የተገነባ፣ የጥራት ምስክርነት በትውልድ አሻራ የተገነባ፣ የጥራት ምስክርነት: ‎‎የደስታ ከረሜላ ፋብሪካ የክብር ጉዞ!…

6 months ago

‎በ 60 ዓመታት የኑሮ ሩጫ ውስጥ ቤተሰብ ከማስተዳደር ባሻገር

‎በ 60 ዓመታት የኑሮ ሩጫ ውስጥ ቤተሰብ ከማስተዳደር ባሻገር በውጤታማ እና ስኬታማ የሥራ ዘመናት የተገነባ…

6 months ago

ጣፋጩ ደስታ ከረሜላ ዳግም ወደ ገበያ ሊመለስ ነዉ !!!!

ጣፋጩ ደስታ ከረሜላ ዳግም ወደ ገበያ ሊመለስ ነዉ !!!! የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ማኔጅመንት የፋብሪካዉን…

1 year ago

አንጋፋዉ ወንጂ ስኳር ፋብሪካ የተመሰረተበትን የ70ኛ አመት በዓል በተለያዩ መርሃ ግብሮች  አክብሯል ::

አንጋፋዉ ወንጂ ስኳር ፋብሪካ የተመሰረተበትን የ70ኛ አመት በዓል በተለያዩ መርሃ ግብሮች አክብሯል :: ፋብሪካዉ  መጋቢት…

1 year ago