Categories: 21/1/2023

የወንጂ/ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ከባንክ ብድር እንዲመቻችለት  የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የአዋጭነት ጥናት ሰነድ እንዲያቀርቡ ሰነድ ተፈራረሙ ፡፡

የወንጂ/ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ከባንክ ብድር እንዲመቻችለት የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የአዋጭነት ጥናት ሰነድ እንዲያቀርቡ ሰነድ ተፈራረሙ ፡፡

የወንጂ/ሸዋ ስኳር ፋብሪካ የሀገሪቱን የስˆር ፍላጎት በማሟላት የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ስኳር እና የተጓዳኝ ምርት በአነስተኛ የማምረቻ ወጪ በማምረት ትርፋማ እና ተወዳዳሪ ስኳር ፋብሪካ ማድረግ ራእይው አድርጎ የተነሳ ሲሆን በቀጣይም የፋይናንስ አቅሙን በማጠናከር ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ለመስራት አቅዷል ፡፡የመንግስት ልዩ ትክረት ያልተለየው የወንጂ/ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ያጋጠመውን የፋይናንስ ምንጭ እጥረት ለመቅረፍ እና የተጀመረውን የፋብሪካውን ተሃድሶ እና መልሶ ግንባታ ስራዎች ማለትም በድሬኔጅ ችግር ምክንያት በውሀ ተበልተው ሸንኮራ አገዳ ሳይለማባቸው የቆዩ ማሳዎች ወደ ልማት መመለስ፣የምርታማነት ችግር ያለባቸውን ማሳዎች ከድሬን ላይ በሚነሳ አፈር የማከም ስራ በሚፈለገው ልክ ለመሰራት፣የግብዓት አቅርቦትና መለዋዋጫ እጥረቶችን ለመቅረፍ፣ የፋብሪካ ተርባይንን ጠግኖ ወደ ስራ በማስገባት በየዓመቱ በሚሊየኖች የሚወጣውን ከፋተኛ የኤሌክትሪካ ወጪ ለመቀነስ ፣ የአገልግሎት ዘመናቸውን የጨረሱ ማሽኖችና ተቀጽላዎችን ለመተካት እና ዋና ዋና የፋብሪካው ማነቆ የሆኑትን ችግሮች ለመቅረፍ ከባንኮች ብድር እንዲመቻችለት የአዋጭነት ጥናት ሰነድ በኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ተጠንቶ ለባንኮች እንዲቀርብ የወንጂ/ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጀማል አማን እና የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አክሊሉ ታደሰ ጋር ጳጉሜ 3/2015 ዓ.ም የስምምነት ሰነድ ተፈራርመዋል ፡፡

wssf

Recent Posts

በትውልድ አሻራ የተገነባ፣ የጥራት ምስክርነት

በትውልድ አሻራ የተገነባ፣ የጥራት ምስክርነት በትውልድ አሻራ የተገነባ፣ የጥራት ምስክርነት: ‎‎የደስታ ከረሜላ ፋብሪካ የክብር ጉዞ!…

6 months ago

‎በ 60 ዓመታት የኑሮ ሩጫ ውስጥ ቤተሰብ ከማስተዳደር ባሻገር

‎በ 60 ዓመታት የኑሮ ሩጫ ውስጥ ቤተሰብ ከማስተዳደር ባሻገር በውጤታማ እና ስኬታማ የሥራ ዘመናት የተገነባ…

6 months ago

ጣፋጩ ደስታ ከረሜላ ዳግም ወደ ገበያ ሊመለስ ነዉ !!!!

ጣፋጩ ደስታ ከረሜላ ዳግም ወደ ገበያ ሊመለስ ነዉ !!!! የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ማኔጅመንት የፋብሪካዉን…

1 year ago

አንጋፋዉ ወንጂ ስኳር ፋብሪካ የተመሰረተበትን የ70ኛ አመት በዓል በተለያዩ መርሃ ግብሮች  አክብሯል ::

አንጋፋዉ ወንጂ ስኳር ፋብሪካ የተመሰረተበትን የ70ኛ አመት በዓል በተለያዩ መርሃ ግብሮች አክብሯል :: ፋብሪካዉ  መጋቢት…

1 year ago