Categories: 21/1/2023

ፋብሪካዉ ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲቲዩት ጋር IS0 9001 – 2015 ለማስጀመር ስምምነት ተፈራረመ

ፋብሪካዉ ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲቲዩት ጋር IS0 9001 - 2015 ለማስጀመር ስምምነት ተፈራረመ

የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ አሰራሩን በአለም አቀፍ ስታንዳርድ መሰረት ለመፈጸም የሚያስችለዉን  እና ፋብሪካውም በቀጣይ ምርቱን በገበያ ላይ አቅርቦ ተወዳዳሪ መሆን የሚያስችለውን የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ISO 9001–2015 ትግበራ ዝግጅት በማጠናቀቅ ወደ ሙሉ ትግበራ ለመግባት የሚያስችል ሥምምነት ሠነድ ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲቲውት ጋር ተፈራርሟል፡፡

የስምምነት ሠነዱን የተፈራረሙት የወንጂ/ሸዋ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጀማል አማን እና የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲቲውት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሰረት በቀለ ናቸው፡፡

በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲቲውት ፋብሪካው የጥራት ስራ አመራር ስርዓትን ለመተግበር እና የእውቅና ሰርተፍኬት ለማግኘት በሚያደርገው ጥረት ላይ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልጸዋል፡፡ የፋብሪካው ዋና ስራ አስኪያጅም ትግበራውን እስከ ታችኛው ሠራተኛ ድረስ በማዉረድ በአጭር ጊዜ መስፈርቱን አሟልተው የእውቅና ሰርተፊኬት በማግኘት የፋብሪካውን ምርት እና አገልግሎት ወደ አለም አቀፍ ስታንዳርድ ለማምጣት እንደሚችሉ ገልጸዋል፡፡

wssf

Recent Posts

በትውልድ አሻራ የተገነባ፣ የጥራት ምስክርነት

በትውልድ አሻራ የተገነባ፣ የጥራት ምስክርነት በትውልድ አሻራ የተገነባ፣ የጥራት ምስክርነት: ‎‎የደስታ ከረሜላ ፋብሪካ የክብር ጉዞ!…

6 months ago

‎በ 60 ዓመታት የኑሮ ሩጫ ውስጥ ቤተሰብ ከማስተዳደር ባሻገር

‎በ 60 ዓመታት የኑሮ ሩጫ ውስጥ ቤተሰብ ከማስተዳደር ባሻገር በውጤታማ እና ስኬታማ የሥራ ዘመናት የተገነባ…

6 months ago

ጣፋጩ ደስታ ከረሜላ ዳግም ወደ ገበያ ሊመለስ ነዉ !!!!

ጣፋጩ ደስታ ከረሜላ ዳግም ወደ ገበያ ሊመለስ ነዉ !!!! የወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ ማኔጅመንት የፋብሪካዉን…

1 year ago

አንጋፋዉ ወንጂ ስኳር ፋብሪካ የተመሰረተበትን የ70ኛ አመት በዓል በተለያዩ መርሃ ግብሮች  አክብሯል ::

አንጋፋዉ ወንጂ ስኳር ፋብሪካ የተመሰረተበትን የ70ኛ አመት በዓል በተለያዩ መርሃ ግብሮች አክብሯል :: ፋብሪካዉ  መጋቢት…

1 year ago